በኢትዮጵያ እስከ ታህሳስ 2011 ዓ.ም የምግብ እህል እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ዜጎች ቁጥር ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ37 በመቶ በመጨመር 7 ነጥብ 8 ሚሊየን መድረሱን መንግሥትና ለጋሾች በትላንትናው ዕለት አስታወቁ፡፡
በዚሁ መሰረት በቀጣይ አንድ ዓመት በድርቅ የተጎዳው ተረጂ ወገን ቁጥር 7 ሚሊየን 880 ሺ 446 መሆኑንና ሰብዓዊ ዕርዳታ ለማቅረብም 1 ነጥብ 4 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር እንደሚያስፈልግ ይፋ ተረጋግጦአል፡፡